Vers | Amharic NT | English: King James Version |
1 | ነገር ግን ከሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ያዘጋጁትን ሽቱ ይዘው ከእነርሱም ጋር አንዳንዶቹ ወደ መቃብሩ እጅግ ማልደው መጡ። | Now upon the first day of the week, very early in the morning, they came unto the sepulchre, bringing the spices which they had prepared, and certain others with them. |
2 | ድንጋዩንም ከመቃብሩ ተንከባሎ አገኙት፥ | And they found the stone rolled away from the sepulchre. |
3 | ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም። | And they entered in, and found not the body of the Lord Jesus. |
4 | እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤ | And it came to pass, as they were much perplexed thereabout, behold, two men stood by them in shining garments: |
5 | ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም። | And as they were afraid, and bowed down their faces to the earth, they said unto them, Why seek ye the living among the dead? |
6 | የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ። | He is not here, but is risen: remember how he spake unto you when he was yet in Galilee, |
8 | ቃሎቹንም አሰቡ፥ ከመቃብሩም ተመልሰው ይህን ሁሉ ለአሥራ አንዱና ለሌሎች ሁሉ ነገሩአቸው። | And they remembered his words, |
10 | ይህንም ለሐዋርያት የነገሩአቸው መግደላዊት ማርያምና ዮሐና የያዕቆብም እናት ማርያም ከእነርሱም ጋር የነበሩት ሌሎች ሴቶች ነበሩ። | It was Mary Magdalene, and Joanna, and Mary the mother of James, and other women that were with them, which told these things unto the apostles. |
11 | ይህም ቃል ቅዠት መስሎ ታያቸውና አላመኑአቸውም። | And their words seemed to them as idle tales, and they believed them not. |
12 | ጴጥሮስ ግን ተነሥቶ ወደ መቃብር ሮጠ፤ በዚያም ዝቅ ብሎ ሲመለከት የተልባ እግር ልብስን ብቻ አየ፤ በሆነውም ነገር እየተደነቀ ወደ ቤቱ ሄደ። | Then arose Peter, and ran unto the sepulchre; and stooping down, he beheld the linen clothes laid by themselves, and departed, wondering in himself at that which was come to pass. |
13 | እነሆም፥ ከእነርሱ ሁለቱ በዚያ ቀን ከኢየሩሳሌም ስድሳ ምዕራፍ ያህል ወደሚርቅ ኤማሁስ ወደሚባል መንደር ይሄዱ ነበር፤ | And, behold, two of them went that same day to a village called Emmaus, which was from Jerusalem about threescore furlongs. |
14 | ስለዚህም ስለ ሆነው ነገር ሁሉ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር። | And they talked together of all these things which had happened. |
15 | ሲነጋገሩና ሲመራመሩም፥ ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር ይሄድ ነበር፤ | And it came to pass, that, while they communed together and reasoned, Jesus himself drew near, and went with them. |
16 | ነገር ግን እንዳያውቁት ዓይናቸው ተይዞ ነበር። | But their eyes were holden that they should not know him. |
17 | እርሱም። እየጠወለጋችሁ ስትሄዱ፥ እርስ በርሳችሁ የምትነጋገሩአቸው እነዚህ ነገሮች ምንድር ናቸው? አላቸው። | And he said unto them, What manner of communications are these that ye have one to another, as ye walk, and are sad? |
18 | ቀለዮጳ የሚባልም አንዱ መልሶ። አንተ በኢየሩሳሌም እንግዳ ሆነህ ለብቻህ ትኖራለህን? በእነዚህ ቀኖች በዚያ የሆነውን ነገር አታውቅምን? አለው። | And the one of them, whose name was Cleopas, answering said unto him, Art thou only a stranger in Jerusalem, and hast not known the things which are come to pass therein these days? |
19 | እርሱም። ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት። በእግዚአብሔርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ፤ | And he said unto them, What things? And they said unto him, Concerning Jesus of Nazareth, which was a prophet mighty in deed and word before God and all the people: |
20 | እርሱንም የካህናት አለቆችና መኳንንቶቻችን ለሞት ፍርድ እንዴት አሳልፈው እንደ ሰጡትና እንደ ሰቀሉት ነው። | And how the chief priests and our rulers delivered him to be condemned to death, and have crucified him. |
21 | እኛ ግን እስራኤልን እንዲቤዥ ያለው እርሱ እንደ ሆነ ተስፋ አድርገን ነበር፤ ደግሞም ከዚህ ሁሉ ጋር ይህ ከሆነ ዛሬ ሦስተኛው ቀን ነው። | But we trusted that it had been he which should have redeemed Israel: and beside all this, to day is the third day since these things were done. |
22 | ደግሞም ከእኛ ውስጥ ማልደው ከመቃብሩ ዘንድ የነበሩት አንዳንድ ሴቶች አስገረሙን፤ | Yea, and certain women also of our company made us astonished, which were early at the sepulchre; |
23 | ሥጋውንም ባጡ ጊዜ። ሕያው ነው የሚሉ የመላእክትን ራእይ ደግሞ አየን ሲሉ መጥተው ነበር። | And when they found not his body, they came, saying, that they had also seen a vision of angels, which said that he was alive. |
24 | ከእኛም ጋር ከነበሩት ወደ መቃብር ሄደው ሴቶች እንደ ተናገሩት ሆኖ አገኙት፥ እርሱን ግን አላዩትም። | And certain of them which were with us went to the sepulchre, and found it even so as the women had said: but him they saw not. |
25 | እርሱም። እናንተ የማታስተውሉ፥ ነቢያትም የተናገሩትን ሁሉ ልባችሁ ከማመን የዘገየ፤ | Then he said unto them, O fools, and slow of heart to believe all that the prophets have spoken: |
26 | ክርስቶስ ይህን መከራ ይቀበል ዘንድና ወደ ክብሩ ይገባ ዘንድ ይገባው የለምን? አላቸው። | Ought not Christ to have suffered these things, and to enter into his glory? |
27 | ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጐመላቸው። | And beginning at Moses and all the prophets, he expounded unto them in all the scriptures the things concerning himself. |
28 | ወደሚሄዱበትም መንደር ቀረቡ፥ እርሱም ሩቅ የሚሄድ መሰላቸው። | And they drew nigh unto the village, whither they went: and he made as though he would have gone further. |
29 | እነርሱ። ከእኛ ጋር እደር፥ ማታ ቀርቦአልና ቀኑም ሊመሽ ጀምሮአል ብለው ግድ አሉት፤ ከእነርሱም ጋር ሊያድር ገባ። | But they constrained him, saying, Abide with us: for it is toward evening, and the day is far spent. And he went in to tarry with them. |
30 | ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጦ ሳለ እንጀራውን አንሥቶ ባረከው፥ ቈርሶም ሰጣቸው፤ | And it came to pass, as he sat at meat with them, he took bread, and blessed it, and brake, and gave to them. |
31 | ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ። | And their eyes were opened, and they knew him; and he vanished out of their sight. |
32 | እርስ በርሳቸውም። በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን? ተባባሉ። | And they said one to another, Did not our heart burn within us, while he talked with us by the way, and while he opened to us the scriptures? |
33 | በዚያችም ሰዓት ተነሥተው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ አሥራ አንዱና ከእነርሱ ጋር የነበሩትም። ጌታ በእውነት ተነሥቶአል ለስምዖንም ታይቶአል እያሉ በአንድነት ተሰብስበው አገኙአቸው። | And they rose up the same hour, and returned to Jerusalem, and found the eleven gathered together, and them that were with them, |
35 | እነርሱም በመንገድ የሆነውን እንጀራውንም በቈረሰ ጊዜ እንዴት እንደ ታወቀላቸው ተረኩላቸው። | And they told what things were done in the way, and how he was known of them in breaking of bread. |
36 | ይህንም ሲነጋገሩ ኢየሱስ ራሱ በመካከላቸው ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው። | And as they thus spake, Jesus himself stood in the midst of them, and saith unto them, Peace be unto you. |
37 | ነገር ግን ደነገጡና ፈሩ መንፈስም ያዩ መሰላቸው። | But they were terrified and affrighted, and supposed that they had seen a spirit. |
38 | እርሱም። ስለ ምን ትደነግጣላችሁ? ስለ ምንስ አሳብ በልባችሁ ይነሣል? | And he said unto them, Why are ye troubled? and why do thoughts arise in your hearts? |
39 | እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው። | Behold my hands and my feet, that it is I myself: handle me, and see; for a spirit hath not flesh and bones, as ye see me have. |
40 | ይህንም ብሎ እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው። | And when he had thus spoken, he shewed them his hands and his feet. |
41 | እነርሱም ከደስታ የተነሣ ገና ስላላመኑ ሲደነቁ ሳሉ። በዚህ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው። | And while they yet believed not for joy, and wondered, he said unto them, Have ye here any meat? |
42 | እነርሱም ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቁራጭ፥ ከማር ወለላም ሰጡት፤ | And they gave him a piece of a broiled fish, and of an honeycomb. |
43 | ተቀብሎም በፊታቸው በላ። | And he took it, and did eat before them. |
44 | እርሱም። ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው። | And he said unto them, These are the words which I spake unto you, while I was yet with you, that all things must be fulfilled, which were written in the law of Moses, and in the prophets, and in the psalms, concerning me. |
45 | በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤ | Then opened he their understanding, that they might understand the scriptures, |
46 | እንዲህም አላቸው። ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥ | And said unto them, Thus it is written, and thus it behoved Christ to suffer, and to rise from the dead the third day: |
47 | በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል። | And that repentance and remission of sins should be preached in his name among all nations, beginning at Jerusalem. |
48 | እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ። | And ye are witnesses of these things. |
49 | እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ። | And, behold, I send the promise of my Father upon you: but tarry ye in the city of Jerusalem, until ye be endued with power from on high. |
50 | እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው። | And he led them out as far as to Bethany, and he lifted up his hands, and blessed them. |
51 | ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ። | And it came to pass, while he blessed them, he was parted from them, and carried up into heaven. |
52 | እነርሱም፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ | And they worshipped him, and returned to Jerusalem with great joy: |
53 | ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ። | And were continually in the temple, praising and blessing God. Amen. |
7 | Saying, The Son of man must be delivered into the hands of sinful men, and be crucified, and the third day rise again. | |
9 | And returned from the sepulchre, and told all these things unto the eleven, and to all the rest. | |
34 | Saying, The Lord is risen indeed, and hath appeared to Simon. |