Vers | Amharic NT | English: King James Version |
1 | እንግዲህ የአይሁዳዊ ብልጫው ምንድር ነው? ወይስ የመገረዝ ጥቅሙ ምንድር ነው? በሁሉ ነገር ብዙ ነው። | What advantage then hath the Jew? or what profit is there of circumcision? |
2 | አስቀድሞ የእግዚአብሔር ቃላት አደራ ተሰጡአቸው። ታዲያ ምንድር ነው? | Much every way: chiefly, because that unto them were committed the oracles of God. |
3 | የማያምኑ ቢኖሩ አለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀራልን? | For what if some did not believe? shall their unbelief make the faith of God without effect? |
4 | እንዲህ አይሁን፤ በቃልህ ትጸድቅ ዘንድ ወደ ፍርድ በገባህም ጊዜ ትረታ ዘንድ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ሰው ሁሉ ውሸተኛ ከሆነ እግዚአብሔር እውነተኛ ይሁን። | God forbid: yea, let God be true, but every man a liar; as it is written, That thou mightest be justified in thy sayings, and mightest overcome when thou art judged. |
5 | ነገር ግን ዓመፃችን የእግዚአብሔርን ጽድቅ የሚያስረዳ ከሆነ ምን እንላለን? ቍጣን የሚያመጣ እግዚአብሔር ዓመፀኛ ነውን? እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። | But if our unrighteousness commend the righteousness of God, what shall we say? Is God unrighteous who taketh vengeance? (I speak as a man) |
6 | እንዲህ አይሁን፤ እንዲህ ቢሆን እግዚአብሔር በዓለም እንዴት ይፈርዳል? | God forbid: for then how shall God judge the world? |
7 | በእኔ ውሸት ግን የእግዚአብሔር እውነት ለክብሩ ከላቀ ስለምን በእኔ ደግሞ እንደ ኃጢአተኛ ገና ይፈርድብኛል? | For if the truth of God hath more abounded through my lie unto his glory; why yet am I also judged as a sinner? |
8 | ስለ ምንስ መልካም እንዲመጣ ክፉ አናደርግም? እንዲሁ ይሰድቡናልና አንዳንዱም እንዲሁ እንድንል ይናገራሉና። የእነርሱም ፍርድ ቅን ነው። | And not rather, (as we be slanderously reported, and as some affirm that we say,) Let us do evil, that good may come? whose damnation is just. |
9 | እንግዲህ ምን ይሁን? ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም ሁሉ ከኃጢአት በታች እንደ ሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋልና፤ | What then? are we better than they? No, in no wise: for we have before proved both Jews and Gentiles, that they are all under sin; |
10 | እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ። | As it is written, There is none righteous, no, not one: |
11 | ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥ | There is none that understandeth, there is none that seeketh after God. |
12 | በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም። | They are all gone out of the way, they are together become unprofitable; there is none that doeth good, no, not one. |
13 | ጕሮሮአቸው እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፥ በመላሳቸውም ሸንግለዋል፤ የእባብ መርዝ ከከንፈሮቻቸው በታች አለ፤ | Their throat is an open sepulchre; with their tongues they have used deceit; the poison of asps is under their lips: |
14 | አፋቸውም እርግማንና መራርነት ሞልቶበታል፤ | Whose mouth is full of cursing and bitterness: |
15 | እግሮቻቸው ደምን ለማፍሰስ ፈጣኖች ናቸው፤ | Their feet are swift to shed blood: |
16 | ጥፋትና ጉስቁልና በመንገዳቸው ይገኛል፥ | Destruction and misery are in their ways: |
17 | የሰላምንም መንገድ አያውቁም። በዓይኖቻቸው ፊት እግዚአብሔርን መፍራት የለም። | And the way of peace have they not known: |
19 | አፍም ሁሉ ይዘጋ ዘንድ ዓለምም ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች ይሆን ዘንድ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንዲናገር እናውቃለን፤ | Now we know that what things soever the law saith, it saith to them who are under the law: that every mouth may be stopped, and all the world may become guilty before God. |
20 | ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። | Therefore by the deeds of the law there shall no flesh be justified in his sight: for by the law is the knowledge of sin. |
21 | አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ | But now the righteousness of God without the law is manifested, being witnessed by the law and the prophets; |
22 | እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ | Even the righteousness of God which is by faith of Jesus Christ unto all and upon all them that believe: for there is no difference: |
23 | ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ | For all have sinned, and come short of the glory of God; |
24 | በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ። | Being justified freely by his grace through the redemption that is in Christ Jesus: |
25 | እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለ መተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፥ | Whom God hath set forth to be a propitiation through faith in his blood, to declare his righteousness for the remission of sins that are past, through the forbearance of God; |
26 | ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው። | To declare, I say, at this time his righteousness: that he might be just, and the justifier of him which believeth in Jesus. |
27 | ትምክህት እንግዲህ ወዴት ነው? እርሱ ቀርቶአል። በየትኛው ሕግ ነው? በሥራ ሕግ ነውን? አይደለም፥ በእምነት ሕግ ነው እንጂ። | Where is boasting then? It is excluded. By what law? of works? Nay: but by the law of faith. |
28 | ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና። | Therefore we conclude that a man is justified by faith without the deeds of the law. |
29 | ወይስ እግዚአብሔር የአይሁድ ብቻ አምላክ ነውን? የአሕዛብስ ደግሞ አምላክ አይደለምን? አዎን፥ የተገረዘን ስለ እምነት ያልተገረዘንም በእምነት የሚያጸድቅ አምላክ አንድ ስለ ሆነ የአሕዛብ ደግሞ አምላክ ነው። | Is he the God of the Jews only? is he not also of the Gentiles? Yes, of the Gentiles also: |
31 | እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም፤ ሕግን እናጸናለን እንጂ። | Do we then make void the law through faith? God forbid: yea, we establish the law. |
18 | There is no fear of God before their eyes. | |
30 | Seeing it is one God, which shall justify the circumcision by faith, and uncircumcision through faith. |