Vers | Amharic NT | English: King James Version |
1 | በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታንም ባነሣው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆነ እንጂ ከሰዎች ወይም በሰው ያልሆነ ጳውሎስ ከእኔም ጋር ያሉት ወንድሞች ሁሉ፥ ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናት፤ | Paul, an apostle, (not of men, neither by man, but by Jesus Christ, and God the Father, who raised him from the dead;) |
3 | ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። | Grace be to you and peace from God the Father, and from our Lord Jesus Christ, |
4 | ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ። | Who gave himself for our sins, that he might deliver us from this present evil world, according to the will of God and our Father: |
5 | ለአብ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። | To whom be glory for ever and ever. Amen. |
6 | በክርስቶስ ጸጋ እናንተን ከጠራችሁ ከእርሱ ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ፤ | I marvel that ye are so soon removed from him that called you into the grace of Christ unto another gospel: |
7 | እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ። | Which is not another; but there be some that trouble you, and would pervert the gospel of Christ. |
8 | ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። | But though we, or an angel from heaven, preach any other gospel unto you than that which we have preached unto you, let him be accursed. |
9 | አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። | As we said before, so say I now again, If any man preach any other gospel unto you than that ye have received, let him be accursed. |
10 | ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም። | For do I now persuade men, or God? or do I seek to please men? for if I yet pleased men, I should not be the servant of Christ. |
11 | ወንድሞች ሆይ፥ በእኔ የተሰበከ ወንጌል እንደ ሰው እንዳይደለ አስታውቃችኋለሁ፤ | But I certify you, brethren, that the gospel which was preached of me is not after man. |
12 | ኢየሱስ ክርስቶስ ገልጦልኛል እንጂ እኔ ከሰው አልተቀበልሁትም አልተማርሁትምም። | For I neither received it of man, neither was I taught it, but by the revelation of Jesus Christ. |
13 | በአይሁድ ሥርዓት በፊት እንዴት እንደ ኖርሁ ሰምታችኋልና፤ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ያለ ልክ አሳድድና አጠፋ ነበር፥ | For ye have heard of my conversation in time past in the Jews' religion, how that beyond measure I persecuted the church of God, and wasted it: |
14 | ለአባቶችም ወግ ከመጠን ይልቅ እየቀናሁ በወገኔ ዘንድ በዘመኔ ካሉት ብዙዎችን በአይሁድ ሥርዓት እበልጥ ነበር። | And profited in the Jews' religion above many my equals in mine own nation, being more exceedingly zealous of the traditions of my fathers. |
15 | ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም፥ | But when it pleased God, who separated me from my mother's womb, and called me by his grace, |
17 | ከእኔም በፊት ሐዋርያት ወደ ነበሩት ወደ ኢየሩሳሌም አልወጣሁም፥ ነገር ግን ወደ ዓረብ አገር ሄድሁ እንደ ገናም ወደ ደማስቆ ተመለስሁ። | Neither went I up to Jerusalem to them which were apostles before me; but I went into Arabia, and returned again unto Damascus. |
18 | ከዚህ ወዲያ ከሦስት ዓመት በኋላ ኬፋን ልጠይቅ ወደ ኢየሩሳሌም ወጥቼ ከእርሱ ጋር አሥራ አምስት ቀን ሰነበትሁ፤ | Then after three years I went up to Jerusalem to see Peter, and abode with him fifteen days. |
19 | ነገር ግን ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ በቀር ከሐዋርያት ሌላ አላየሁም። | But other of the apostles saw I none, save James the Lord's brother. |
20 | ስለምፅፍላችሁም ነገር፥ እነሆ፥ በእግዚአብሔር ፊት ሐሰት አልናገርም። | Now the things which I write unto you, behold, before God, I lie not. |
21 | ከዚያ ወዲያ ወደ ሶርያና ወደ ኪልቅያ አገር መጣሁ። | Afterwards I came into the regions of Syria and Cilicia; |
22 | በክርስቶስም ያሉት የይሁዳ ማኅበሮች ፊቴን አያውቁም ነበር፤ | And was unknown by face unto the churches of Judaea which were in Christ: |
23 | ነገር ግን። ቀድሞ እኛን ያሳድድ የነበረ፥ እርሱ በፊት ያጠፋው የነበረውን ሃይማኖት አሁን ይሰብካል ተብሎ ሲነገር ይሰሙ ነበር፤ | But they had heard only, That he which persecuted us in times past now preacheth the faith which once he destroyed. |
24 | ስለ እኔም እግዚአብሔርን ያከብሩ ነበር። | And they glorified God in me. |
2 | And all the brethren which are with me, unto the churches of Galatia: | |
16 | To reveal his Son in me, that I might preach him among the heathen; immediately I conferred not with flesh and blood: |