Vers | Amharic NT | English: King James Version |
1 | ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤ | But of the times and the seasons, brethren, ye have no need that I write unto you. |
2 | የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና። | For yourselves know perfectly that the day of the Lord so cometh as a thief in the night. |
3 | ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም። | For when they shall say, Peace and safety; then sudden destruction cometh upon them, as travail upon a woman with child; and they shall not escape. |
4 | እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥ | But ye, brethren, are not in darkness, that that day should overtake you as a thief. |
5 | ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤ | Ye are all the children of light, and the children of the day: we are not of the night, nor of darkness. |
6 | እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ። | Therefore let us not sleep, as do others; but let us watch and be sober. |
7 | የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤ | For they that sleep sleep in the night; and they that be drunken are drunken in the night. |
8 | እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤ | But let us, who are of the day, be sober, putting on the breastplate of faith and love; and for an helmet, the hope of salvation. |
9 | እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ። | For God hath not appointed us to wrath, but to obtain salvation by our Lord Jesus Christ, |
10 | የምንነቃም ብንሆን፥ የምናንቀላፋም ብንሆን፥ ከእርሱ ጋር አብረን በሕይወት እንኖር ዘንድ ስለ እኛ ሞተ። | Who died for us, that, whether we wake or sleep, we should live together with him. |
11 | ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው። | Wherefore comfort yourselves together, and edify one another, even as also ye do. |
12 | ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ። | And we beseech you, brethren, to know them which labour among you, and are over you in the Lord, and admonish you; |
14 | ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ። | Now we exhort you, brethren, warn them that are unruly, comfort the feebleminded, support the weak, be patient toward all men. |
15 | ማንም ለሌላው በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፥ ነገር ግን ሁልጊዜ እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ። | See that none render evil for evil unto any man; but ever follow that which is good, both among yourselves, and to all men. |
16 | ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ | Rejoice evermore. |
17 | ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና። | Pray without ceasing. |
19 | መንፈስን አታጥፉ፤ | Quench not the Spirit. |
20 | ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤ | Despise not prophesyings. |
22 | ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ። | Abstain from all appearance of evil. |
23 | የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ። | And the very God of peace sanctify you wholly; and I pray God your whole spirit and soul and body be preserved blameless unto the coming of our Lord Jesus Christ. |
24 | የሚጠራችሁ የታመነ ነው፥ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል። | Faithful is he that calleth you, who also will do it. |
25 | ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ። | Brethren, pray for us. |
26 | ከወንድሞች ሁሉ ጋር በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ። | Greet all the brethren with an holy kiss. |
27 | ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ። | I charge you by the Lord that this epistle be read unto all the holy brethren. |
28 | የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን። | The grace of our Lord Jesus Christ be with you. Amen. |
13 | And to esteem them very highly in love for their work's sake. And be at peace among yourselves. | |
18 | In every thing give thanks: for this is the will of God in Christ Jesus concerning you. | |
21 | Prove all things; hold fast that which is good. |