Vers | Amharic NT | English: King James Version |
1 | ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤ | Wherefore, holy brethren, partakers of the heavenly calling, consider the Apostle and High Priest of our profession, Christ Jesus; |
2 | ሙሴ ደግሞ በቤቱ ሁሉ የታመነ እንደሆነ፥ እርሱ ለሾመው የታመነ ነበረ። | Who was faithful to him that appointed him, as also Moses was faithful in all his house. |
3 | ቤትን የሚያዘጋጀው ከቤቱ ይልቅ የሚበልጥ ክብር እንዳለው መጠን፥ እንዲሁ እርሱ ከሙሴ ይልቅ የሚበልጥ ክብር የተገባው ሆኖ ተቆጥሮአልና። | For this man was counted worthy of more glory than Moses, inasmuch as he who hath builded the house hath more honour than the house. |
4 | እያንዳንዱ ቤት በአንድ ሰው ተዘጋጅቶአልና፥ ሁሉን ያዘጋጀ ግን እግዚአብሔር ነው። | For every house is builded by some man; but he that built all things is God. |
5 | ሙሴስ በኋላ ስለሚነገረው ነገር ምስክር ሊሆን በቤቱ ሁሉ እንደ ሎሌ የታመነ ነበረ፥ ክርስቶስ ግን እንደ ልጅ በቤቱ ላይ የታመነ ነው፤ | And Moses verily was faithful in all his house, as a servant, for a testimony of those things which were to be spoken after; |
6 | እኛም የምንደፍርበትን የምንመካበትንም ተስፋ እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ ቤቱ ነን። | But Christ as a son over his own house; whose house are we, if we hold fast the confidence and the rejoicing of the hope firm unto the end. |
7 | ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚል። | Wherefore (as the Holy Ghost saith, To day if ye will hear his voice, |
8 | ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት፥ አባቶቻችሁ እኔን የፈተኑበት የመረመሩበትም አርባ ዓመትም ሥራዬን ያዩበት በምድረ በዳ በፈተና ቀን በማስመረር እንደ ሆነ፥ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ። | Harden not your hearts, as in the provocation, in the day of temptation in the wilderness: |
10 | ስለዚህ ያን ትውልድ ተቆጥቼ። ዘወትር በልባቸው ይስታሉ መንገዴን ግን አላወቁም አልሁ፤ | Wherefore I was grieved with that generation, and said, They do alway err in their heart; and they have not known my ways. |
11 | እንዲሁ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቍጣዬ ማልሁ። | So I sware in my wrath, They shall not enter into my rest.) |
12 | ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤ | Take heed, brethren, lest there be in any of you an evil heart of unbelief, in departing from the living God. |
13 | ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፥ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፥ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ፤ | But exhort one another daily, while it is called To day; lest any of you be hardened through the deceitfulness of sin. |
14 | የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና፤ | For we are made partakers of Christ, if we hold the beginning of our confidence stedfast unto the end; |
15 | እየተባለ። ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ። | While it is said, To day if ye will hear his voice, harden not your hearts, as in the provocation. |
16 | ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ? በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን? | For some, when they had heard, did provoke: howbeit not all that came out of Egypt by Moses. |
17 | አርባ አመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ፥ ኃጢአትን ያደረጉት እነርሱ አይደሉምን? | But with whom was he grieved forty years? was it not with them that had sinned, whose carcases fell in the wilderness? |
18 | ካልታዘዙትም በቀር ወደ እረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ? | And to whom sware he that they should not enter into his rest, but to them that believed not? |
19 | ባለማመናቸውም ጠንቅ ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን። | So we see that they could not enter in because of unbelief. |
9 | When your fathers tempted me, proved me, and saw my works forty years. |